የክሪስታል ፓላሱ ግብ ጠባቂ ዲን ሄንደርሰን የኤፌ ካፕ ዋንጫን የማንሳት ህልሙ እውን ቢሆን ኖሮ በህይወት ላጡት ወላጅ አባቱ መታሰቢያ እንዲሆን እንደሚፈልግ ተናግሯል።
በውድድር ዓመቱ መጀመሪያ ላይ አባቱን በሞት እንዳጣ በሀዘን የገለጸው ሄንደርሰን “ዛሬ እዚህ እንዲኖር በእውነት እመኝ ነበር” ሲል በቁጭት ተናግሯል።
ሄንደርሰን አክሎም “ወላጅ አባቴ በእያንዳንዱ የህይወቴ ቅጽበት ከእኔ ጋር ነው፤ ይህ ዋንጫ ለእሱ የዘላለም መታሰቢያ ይሁንልኝ” ሲል ልባዊ ስሜቱን ተናግሯል።
በተጨማሪም ሄንደርሰን ስለ ዑመር መርሙሽ የፍፁም ቅጣት ምት ሲናገር “ዑመር መርሙሽ ኳሱን በየት በኩል እንደሚመታ እና እኔም እንዴት እንደምመልሰው አስቀድሜ በልቤ አውቄ ነበር” ብሏል።